|
ማስታወቂያ
ለአገልግሎት ጠያቂዎች በሙሉ
በስቶክሆልም የሚገኘው የኢትዮጵያ ቆንስላ ፅ/ቤት ከመስከረም 01 ቀን 2003 ዓም ጀምሮ የአገልግሎት አሰጣጥ
ማሻሻያና ለውጥ ያደርጋል፡፡
በመሆኑም ማንኛውም ተገልጋይ ወደ ቆንስላ ፅ/ቤቱ በአካል ከመምጣቱ በፊት ለሚፈልገው ማንኛውም ግልጋሎት
በቆንስላ ጽ/ቤቱ የተዘጋጀውን የአገልግሎት መስጫ ቅፅ በቅድሚያ ከቆንስላ ጽ/ቤቱ ድረ-ገፅ
www.ethemb.se
በማውጣት በመሙላት ይዞ መቅረብ ይጠበቅበታል፡፡
የኢትዮጵያ ኤምባሲ
ስቶክሆልም
|
|
Ethiopian Embassy in Stockholm, Sweden is also
Accredited to Denmark,
Finland, Iceland, Norway.
ለማንኛውም አገልግሎት
ክፍያ በስዊድን ክሮነር
መፈፀም የሚኖርበት ሲሆን ክፍያው በኤምባሲው
Postgiro No.
629247-8 ወይም የባንክ
አካውንት
(Nordea Bank
IBAN No. SE62 9500 0099 6026 0629 2478, SWIFT-Code NDEASESS)
ተገልጋዩ ወደ
ቆንስላ ፅ/ቤቱ ከሚመጣበት ቀን
ከ5 ቀን አስቀድሞ
መከፈል
ይኖርበታል፡፡
Visiting address:
Ethiopian
Embassy
Löjtnantsgatan 17, 5th floor
115 50 Stockholm, Sweden
Contact Address:
Telephone:
+46-8-6616325
Fax:
004686608177
Email:
ethemb.community@telia.com
website:
www.ethemb.se,
Office Hours for
consular section
Visiting Hours:
between 09:00 to 12:00 Monday to
Friday.
Telephone Hours: between 13:30
- 15:30 Monday to Friday
|
|
Announcement
The Ethiopian
Consulate Office in Stockholm will change its procedures of service
delivering as of September 11, 2010.
Therefore, all
applicants who are coming in person to the Consulate office for any
service should have to fill the application form in advance for
their required services. Application forms can be found on the
Consulate office website, which is
www.ethemb.se.
Ethiopian
Consulate
Stockholm
|
|
ማስታወቂያ
በውጭ ነዋሪ የገቢ ግብር
ከፋዮች በሙሉ
በአገራችን የታክስ አከፋፈል ስርአትን ቀልጣፋና ዘመናዊ ለማድረግ ይቻል ዘንድ ማንኛውም በኢትዮጵያ ውስጥ
በግብር ከፋይነት የሚታወቅ ግለሰብ እስከ ሰኔ 30 ቀን 2002 ዓም ሀገር ውስጥ በአካል በመገኘትና የጣት
አሻራ በመስጠት የታክስ ሰርቲፊኬቱን መውሰድ እንዳለበት መመሪያ መውጣቱ ይታወሳል፡፡
ይሁን
እንጂ በተለያዩ ችግሮች ምክንያት በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ኢትዮጵያ ገቢዎች ባለስልጣን በአካል በመቅረብ
የጣት አሻራ
በመስጠት የታክስ ሰርቲፊኬት መውሰድ ያልቻሉ
ኢትዮጵያውያንና ትውልድ ኢትዮጵያውያን በጠየቁት መሰረት
ቀን ገደብ ወደ ታህሳስ
30 ቀን 2003 ዓም እንዲራዘም ተደርጓል፡፡
በመሆኑም ቀደም ሲል ኤምባሲ ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት የጣት አሻራ ለመስጠት የተመዘገባችሁ እንዲሁም
እስካሁን የታክስ መለያ ቁጥር ያልወሰዳችሁና በአገር ቤት በምታንቀሳቅሱት ቋሚ ወይም ቋሚ ያልሆኑ ንብረት
በማንቀሳቀስ ግብር ከፋይ የሆናችሁ በሙሉ ቀነገደቡ ከመጠናቀቁ በፊት ኢትዮጵያ ገቢዎች ባለስልጣን በአካል
ቀርባችሁ ጣት አሻራ በመስጠት እስከ
መጋቢት
30 ቀን 2003 ዓም
ባለው ጊዜ ውስጥ
የታክስ መክፈያ
ሰርቲፊኬቱን መውሰድ እንደሚገባችሁ ባለስልጣን መ/ቤቱ በድጋሜ ማስታወቁን እናስገነዝባለን፡፡
በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ በአካል ቀርበው
የጣት አሻራ በመስጠት
የታክስ መክፈያ ሰርቲፊኬት ያልወሰዱ የንግድ፣ የኢንቨስትመንት እና ሌሎች ማናቸውም ገቢ ግብር የሚከፈልባቸው
ፍቃዶች የሚሰረዙ መሆኑን
ባለስልጣን መ/ቤቱ
ጨምሮ መግለፁንም በአክብሮት እንገልፃለን፡፡
ተጨማሪ መረጃ
· በስልክ
ቁጥር 004686616158 ወይም በኢሜል
ethemb.community@telia.com
ወይም ስቶክሆልም በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በአካል በመቅረብ ማግኘት ይችላሉ፡፡
የኢትዮጵያ
ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን በጣት አሻራ የተደገፈ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር አሰጣጥ አጭር ማብራሪያ
የኢትዮጵያ ኤምባሲ
ስቶክሆልም
|